Welcome to Lideta Subcity Youth and Sport Office!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ህብረተሰብ እና ተወዳዳሪና ውጤታማ የሆነ ስፖርተኛ ተፈጥሮ ለማየት ይተጋል!!
image
image
image
image
image

በልደታ ክ/ከተማ"ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት ተካሄደ

ህዳር 1, 2018
ፕሮግራሙን የክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። የክ/ከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ጢቂ ድሪባ በፕሮግራሙ ባደረጉት ንግግር ገዥ ትርክትና የሀሳብል ልዕልናን እውን በማድረግ የሀገር ከፍታን ማረጋገጥ አለብን ብለው አንድነትን ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጠናከር የሀገራችንን ብልፅግና ማረጋገጥ ከሁላችንም ይጠበቃል በማለት ገልፀዋል። ገዥ ትርክትን በመገንባት የሀገር ግንባታ ጉዞን ማሳለጥ አለብን ያሉት አቶ ጢቂ በጋራ ትርክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ የብዝሀ ባህል፣ ቅርስና ታሪክ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጲያን ብልፅግና እውን ማድረግ አለብን ሲሉ ገልፀዋል። የወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናተገሩት የማስ ስፖርት ጤናን ከመጠበቅ ባለፈ አንድነትን ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ብለው በዘርፉ ጤናው የተጠበቀ እና ጤናማ አስተሳሰብን የተላበሰ ትውልድ ለመገንባት በትኩረት እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል። ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ዘላቂ ልማትን እውን ለማድረግ ወሳኝ ስለሆነ መሰል ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን እናጠናክራለን ብለዋል አቶ አንተነህ።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች