Welcome to Lideta Subcity Youth and Sport Office!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ህብረተሰብ እና ተወዳዳሪና ውጤታማ የሆነ ስፖርተኛ ተፈጥሮ ለማየት ይተጋል!!
ዜና | Oduu | News
ባለፍት 6 ወራት በስነ-መግባር የታነፀ ብቁ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት መሰራቱን የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ገለፀ።

ባለፍት 6 ወራት በስነ-መግባር የታነፀ ብቁ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት መሰራቱን የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ገለፀ። ጽ/ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወር አፈፃፀሙን ገምግሟል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ በግምገማው ወቅት እንደተናገሩት ባለፍት 6 ወራት ማህበራዊ መስተጋብርን በማጠናከር አንድነት ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን የበለጠ ለማጠናከር በልዩ ትኩረት ተሰርቷል ብለዋል። አቶ አንተነህ አክለውም በስነ-መግባር የታነፀ የሰላም እሴቶቻችን የሚተገብሩ ጤናማ ብቁ ተወዳዳሪና አምራች ዜጋን ለመፍጠር በትኩረት መሰራቱን ገልፀዋል። ስፖርቱ ማህበራዊ መሰረት እንዲኖረው በማድረግ ረገድ ሰፊ ስራ ተሰርቷል ያሉት አቶ አንተነህ በቀጣይም ለዘርፍ እድገት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ ስራዎች በማከናወን ዜጎችን የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ እንሰራለን በማለት ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም ወጣቱ በስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆን የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ምዝገባና የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። ወጣቱን በጎ ፈቃድ ስራዎችን ተሳታፊ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የማድረግ ተግባር መከናወኑን አቶ አንተነህ ገልፀዋል። የስፖርት መሰረተ ልማቶችንም ለማስፋት ከምንጊዜውም በላይ መሰራቱን ኃላፊው ገልፀዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት በ6 ወራት ስፖርት የሁሉም ዜጋ የእለት ከእለት ተግባር እንዲሆን ለማስቻል በዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን መፈጠሩን ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ "ስልጡን ወጣት ለከተማ እድገትና ሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል ከወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ፤

በልደታ ክ/ከተማ "ስልጡን ወጣት ለከተማ እድገትና ሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል ከወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ፤ የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እና የልደታ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ከወጣቶች ጋር ውይይት አካሂዷል። የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክ/ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሰፋ ቶላ እንደገለፁት የሁሉም ነገር መሰረት የሆነውን ሰላም በማስጠበቅ ረገድ ወጣቶች የሚሪነት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ብለው በዚህም ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ወጣቶች የሰላም እሴቶችን በመጠበቅ እና በማስጠበቅ የሀገር ሰላምና ብልፅግና እንዲረጋገጥ የየድርሻቸሁን መወጣት አለባቹህ ብለዋል አቶ አሰፋ። ሰላም የልማቶቻችን ሁሉ መሰረት በመሆኑ እንደ አይናችን ብሌን ልንጠብቀው ይገባል ያሉት አቶ አሰፋ ወጣቶች ከፀጥታ አካሉ ጋር በመቀናጀት ሰላሙን ሊጠብቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናገሩት ስልጡን ወጣት ግጭትን ለመከላከልና ለመፍታት እንዲሁም የረዥም ጊዜ ሰላምና እድገትን ለማስፈን ጠቃሚ ሀይል ነው ብለው ወጣቱ ማህበራዊ ውህደትን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ አቅምን መገንባት አለበት በማለት ተናግረዋል። አቶ አንተነህ አክለውም ስልጡን ወጣት ለከተማ ሰላም ግንባታና ሁለንተናዊ ብልፅግና መሰረት ነው ያሉ ሲሆን ወጣቱ አሰባሳቢ እና ገዥ ትርክትን በማቀንቀን ለሀገር ግንባታ ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። በሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት የሰላም እሴት ግንባታ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ በበኩላቸው ሰላም የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ በጋራ ልንጠብቀው ይገባል ብለዋል። ወጣቶች በበኩላቸው ለሀገር ግንባታና ብልፅግና በትጋት እንሰራለን በማለት ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤትና በአቢሲኒያ ባንክ አዘጋጅነት የእግር ኳስ ውድድር ተጀመረ

በልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤትና በአቢሲኒያ ባንክ አዘጋጅነት የእግር ኳስ ውድድር ተጀመረ በክ/ከተማው አስተባባሪነት ታላቁ የአቢሲኒያ ዋንጫ እንደ ሀገር በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ዲስትሪክቶች ያሳተፈ የእግር ኳስ ውድድር ተጀምሯል። በውድድሩ ማስጀመሪያ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናገሩት የክ/ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት እና አቢሲኒያ ባንክ በስፖርቱ ዘርፍ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውሰው ዛሬ የተጀመረው የእግር ኳስ ውድድርም የዚሁ አካል መሆኑን ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም ስፖርት አንድነትን፣ ወንድማማችነትንና አብሮነትን የሚያጠናክር ነው ብለው በውድድሩ የሚሳተፉ ስፖርተኞችም ስፖርታዊ ጨዋነትን ተላብሰው ማጠናቀቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። የአቢሲኒያ ባንክ የሰው ሀይል አስተዳደር ዋና ኦፊሰር አቶ ሰይፉ ቦጋለ እንደተናገሩት የውድድሩ ዓላማ በሰራተኞች መካከል አንድነትን አብሮነትንና የቡድን ስራን በላቀ በማጠናከር ምርታማነትን ለማሻሻል መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ሰይፉ አክለውም ውድድሩ በ12 ቡድኖች መካከል በ4 ምድብ ተከፍሎ እንደሚካሄድ ገልፀው ውድድሩ ቤተሰባዊነትን በሚያንፀባርቅ መልኩ እንዲጠናቀቅም አሳስበዋል። የአቢሲኒያ ባንክ የሰራተኞች ማህበር ፕሬዜዳንት አቶ ሰለሞን በበኩላቸው ውድድሩ በሰራተኞች መካከል ትብብርና ወዳጅነት የሚገነባበት ነው ብለው ውድድሩም የሰላምን የአንድነትን እና የወንድማማችነት እሴትን የሚያጎለብት እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ያዘጋጀው 16ኛው የባህል ስፖርት ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ያዘጋጀው 16ኛው የባህል ስፖርት ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ። በውድድሩ ላይ በክፍለ ከተማው የሚገኙ አስሩም ወረዳዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ በባህላዊ ስፖርታዊ ጨዋታዎች የታጀበ ትርኢት ቀርቧል። ​የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናገሩት ውድድሩ የተዘጋጀው የባህል ስፖርቶችን በመጠቀም በማህበረሰቡ መካከል ያለውን አንድነትና ወንድማማችነት እና የባህል ልውውጥ የበለጠ ለማጠናከር መሆኑን ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም በውድድሩ በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የባህል ስፖርት ውድድር ክ/ከተማውን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ይመረጣ በማለት ገልፀዋል። በጽ/ቤቱ የስፖርት ማህበራት ባለሙያ የሆኑት አቶ ፍሬው አሎ በበኩላቸው በውድድሩ ምርጥ እና ክፍለ ከተማውን ወክለው በከተማ አቀፍ የባህል ስፖርት ውድድር የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ለመምረጥ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። ​በፌስቲቫሉ ላይ ስድስት የባህል ስፖርት አይነቶች ለውድድር ቀርበዋል። ​ገበጣ፡ (ባለ 12 እና ባለ 18 ቀዳዳ)፣ ቡብ፣​ ሻህ፣ ​ኩርቦና ቀስት ውርወራ የውድድሩ አካል ናቸው። ውድድሩ ወጣቶች የየአካባቢያቸውን የባህል እሴቶች የሚያንፀባርቁበትና እርስ በርስ የሚቀራረቡበት መድረክ ሆኖ ማለፉም ተገልጿል። በውድድሩ ብልጫ ያሳዩ ስፖርተኞች በቀጣይ ለሚካሄደው የከተማ አቀፍ ውድድር ዝግጅታቸውን እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በሌሎች የልማት ስራዎች ያስመዘገብነውን ምርጥ ተሞክሮ በስራ ዕድል ፈጠራም መድገም ያስፈልጋል ሲል የልደታ ክ/ከተማ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ገለፀ!

በሌሎች የልማት ስራዎች ያስመዘገብነውን ምርጥ ተሞክሮ በስራ ዕድል ፈጠራም መድገም ያስፈልጋል ሲል የልደታ ክ/ከተማ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ገለፀ ማህበሩ የስራ ዕድል ፈጠራን ውጤታማ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል። በውይይቱ ተገኝቶ ንግግር ያደረገው የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ምክትል ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ተከስተ አያሌው እንደገለፀው መንግስት ለስራ ዕድል ፈጠራ ምቹ መድላድልን ዘርግቶልናል ብሎ ወጣቶች የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ገልጿል። የልደታ ክ/ከተማ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ቢኒያም አሸናፊ በበኩሉ በሌሎች የልማት ስራዎች ያገኘነውን ተሞክሮ በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ መድገም ይኖርብናል በማለት ገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ስፖርት የቱሪዝም ማዕከል እንዲሆን በትኩረት እየሰራን ነው-የልደታ ክ/ከተማ ስፖርት ምክር ቤት

ምክር ቤቱ የ2018 ዓ.ም 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል። የቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀመጡት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ስፖርት የቱሪዝም ማዕከል ሆኖ የሚጎበኝ እና ልምድ የሚወሰድበት እንዲሆን በትኩረት እየሰራን ነው ብለው ይህ ግብ እንዲሳካም ሁሉም በትኩረት ሊሰራ ይገባል በማለት ገልፀዋል። የስልጠና ማዕከላትን ማጠናከር ፣ ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ መገንባት እና ስፖርቱ ለስራ ዕድል ፈጠራ አጋዥ እንዲሆን ማስቻል በ2018 በጀት ዓመት በትኩረት እየተሰራበት መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በቀጣይም በላቀ እንደሚተገበር ተናግረዋል። ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት፣ የአካል ጉዳተኞችንና መስማት የተሳናቸውን ዜጎች፣ ወጣቶች፣ ታዳጊዎችና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የስፖርት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የበጀት ዓመቱ ትኩረት መሆኑንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በማጠቃለያው ተናግረዋል። በማዘውተሪያ ስፍራዎች የማህበረሰቡን ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው የተያዙ ግቦች እንዲሳኩ ከምንጊዜውም በላይ በትኩረት እንሰራለን በማለት ተናግረዋል። በዕለቱም በዘርፉ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት የዋንጫ ሽልማት ተሰጥቷል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ።

የክፍለ ከተማው የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ና በልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት በጋራ በተዘጋጀው መድረክ ከሁሉም ወረዳዎች ለተውጣጡ ወጣቶች በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። የምክክር መድረኩን የመሩት የክ/ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ፍታለው ከፍያለው ሲሆኑ ይህ የምክክር መድረክ የተዘጋደበት ዋነኛ አላማ ወጣቶችን የሰላም ግንባታ ዋነኛ አካል አድርጎ በማሳተፍ ረገድ ጉልህ እርምጃ መሆኑን በመድረኩ ተመላክቷል። ወጣቶች በሰላም እሴት ግንባታ መጎልበት ዙሪያ ያላቸው ሚና የጉላ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ወጣቶች የሰላም ግንባታ ጥረቶችን በማጠናከር ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። የምክክር መድረኩ በሰላም እሴት ዙሪያ ያላቸውን አዎንታዊ ተፅዕኖ በማጎልበት የሰላም ባህልን ለማስፋፋት እንደሚያግዝ መሆኑ ተብራርቷል። የምክክሩ ተሳታፊ ወጣቶች እንደገለፁት በሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ያላቸውን ሚና በጥልቀት እንዲገነዘቡና ለሰላም ሁለንተናዊ አቅማቸውን እንዲወጡ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በ12ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ልደታ ክፍለ ከተማ ሴቶች አርባምንጭ ከተማን 4ለ2 አሸነፈ።

ልደታ ክ/ከተማ 4-2 አርባ ምንጭ ከተማ 7' ቃልኪዳን ጥላሁን (ፍ)  23' መሰረት ማቴዎስ 45+1 ሄለን እሸቱ            50' ፍሬይወት በድሉ 88' ረድኤት ዳንኤል 90+5' ሰብለወንጌል ወዳጆ። አበበ ቢቂላ ስታዲየም

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ የታዳጊ ወጣቶች የጤና ምርመራ መካሄድ ጀመረ

የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት  የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ስልጠና ፕሮጀክት ልማት ስልጠና ጣቢያ ሰልጣኞች የጤና እና የእድሜ ምርመራ  አካሄደ ጽ/ቤቱ በቢሪሞ ሜዳ ያስጀመረው ምርመራ የጥርስ ጤንነት እና የአካላዊ ቁመና ጤነኝነት በመለካት የሰውነት መጠነ ዙሪያ ምርመራ መሆኑ ተመልክቷል ተተኪ ሰፓርተኞች በብዛትና በጥራት ለማፍራት ከሚደረጉ ዙርፈ ብዙ እንቅስቃሴ አንዱ  የታዳጊ ወጣቶች የጤና ምርመራ መሆኑን የስፓርት ትምህርትና ስልጠና ቡድን መሪ ወ/ሪት እየሩሳሌም ያቆብ ገልጸዋል ምርመራው ለታዳጊ ወጣቶች የአመጋገብ ሁኔታ እና አካላዊ ጤንነታቸውን ለማየት የሚያስችል መሆኑን የገለጹት የከተማ ቢሮ የሕክምና ቡድን መሪ ወይዘሮ ሐያት ኪያር  የተተኪ ስፓርተኞችን ዕድሜ ምርመራ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መካሄድ እንዳለበት ገልጸው የልደታን ስራ አድንቀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ የሳዳት ጀማል መታሰቢያ የእግር ኳስ ውድድር ተጀመረ

የሳዳት ጀማል መታሰቢያ የጤና ቡድን የእግር ኳስ ውድድሩን የልደታ ክ/ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከስፖርት ለሁሉም ኮሚቴ ጋር በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን በውድድሩ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ታዋቂ 8 የጤና የእግር ኳስ ቡድኖች ይሳተፉበታል። በውድድሩ ማስጀመሪያ የቀድሞው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ፍቅሩ ተፈራ፣ ጌታቸው ካሳ (ቡቡ)፣ ፋሲል አብርሃ ፣ በኢትዮጲያ የመጀመሪያው የቅርፅ ውድድር ሻምፒዮን ሀብትሽ ፊትነስ እና ሌሎችም ስመ- ጥር ስፖርተኞች ተገኝተዋል። የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ተገኝተው ባስተላለፍት መልዕክት እንደተናገሩት ሳዳት ጀማል በኢትዮጲያ ብሄራዊ ቡድን በግብ ጠባቂነትና በአሰልጣኝነት በመሳተፍ ለኢትዮጲያ እግር ኳስ አሻራውን ያሳረፈ ተጨዋች ነበረ ብለው ውድድሩም ይህንን የሀገር ባለውለታ ለመዘከር መዘጋጀቱን ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም በውድድሩ ሳዳት ጀማልን ከማስታወስ በተጨማሪ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የጤና ቡድኖች መካከል አንድነትን፣ ወንድማማችነትንና አብሮነትን ለማጠናከርም ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀው ውድድሩ ስፖርታዊ ጨዋነትን ተላብሶ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የየድርሻውን እንዲወጣ መልዕክት አስተላልፈዋል። የስፖርት ለሁሉም ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ስክንድር ጋሻው በበኩላቸው ትልቅ ዓላማ ያለው የሳዳት ጀማል መታሰቢያ ውድድር ስፖርታዊ ጨዋነትን ተላብሶ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ አስተዋፆ እንዲያደርግ አሳስበዋል። የስፖርት ለሁሉም ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ማስተር በፍቃዱ ታደሰ(ኢሱዬ) በበኩላቸው የሳዳት ጀማል መታሰቢያ የእግር ኳስ ውድድር ለ1 ወር የሚቆይ መሆኑን ገልፀው ውድድሩም በስኬት እንዲጠናቀቅም ሁሉም የየድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ"ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት ተካሄደ

ፕሮግራሙን የክ/ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል። የክ/ከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ጢቂ ድሪባ በፕሮግራሙ ባደረጉት ንግግር ገዥ ትርክትና የሀሳብል ልዕልናን እውን በማድረግ የሀገር ከፍታን ማረጋገጥ አለብን ብለው አንድነትን ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጠናከር የሀገራችንን ብልፅግና ማረጋገጥ ከሁላችንም ይጠበቃል በማለት ገልፀዋል። ገዥ ትርክትን በመገንባት የሀገር ግንባታ ጉዞን ማሳለጥ አለብን ያሉት አቶ ጢቂ በጋራ ትርክቶች ላይ ትኩረት በማድረግ የብዝሀ ባህል፣ ቅርስና ታሪክ ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጲያን ብልፅግና እውን ማድረግ አለብን ሲሉ ገልፀዋል። የወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናተገሩት የማስ ስፖርት ጤናን ከመጠበቅ ባለፈ አንድነትን ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ብለው በዘርፉ ጤናው የተጠበቀ እና ጤናማ አስተሳሰብን የተላበሰ ትውልድ ለመገንባት በትኩረት እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል። ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ዘላቂ ልማትን እውን ለማድረግ ወሳኝ ስለሆነ መሰል ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን እናጠናክራለን ብለዋል አቶ አንተነህ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
"በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" በልደታ ክ/ከተማ ዘመናዊ እና ዓለም አቀፍ ስንታንዳርድን የሚያሟላ የስፖርት ማዕከል ስራ ጀመረ

የስፖርት ማከሉ ከሌሎች የስፖርት ማዕከላት ለየት የሚያደርገው ራሱን የቻለ አይስ ባዝ ያለው በመሆኑ ነው። የስፖርት ማዕከሉ ብቁ ፣ ጤናማ ፣ተወዳዳሪ እና አምራች የሆነ አገልጋይ ለመፍጠር ታልሞ የተገነባ ነው።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በ15ኛው ከተማ አቀፍ የአካል ጉዳተኞችና መስማት የተሳናቸው ስፖርታዊ ውድድርና ፌስቲቫል ተሳታፊ የነበረው የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች 2ኛ ደረጃ በመያዝ ተሸላሚ ሆነ።

እንኳን ደስ አላቹህ!! 27 ወርቅ፣ 18 ብር እና 12 የነሀስ መዳሊያዎች በመሰብሰብ የልደታ ክ/ከተማ 2ኛ ሆኖ ወድድሩን አጠናቋል። የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በሽብርቅ ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች 1ኛ ሆኖ አጠናቋል። በተገኘው ውጤት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ይህ ውጤት እንዲመጣ ስትሰሩ ለነበራቹህ እና ለክፍለ ከተማው ነዋሪዎች እንኳን ደስ አላቹህ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም "በአዲስ ዕይታ የልደታን ከፍታ ማረጋገጥ" የሚል መርህን ይዘን በሁሉም ዘርፍ ውጤት ለማምጣት እየሰራን ነው ብለዋል። ክ/ከተማው 16ኛውን መስማት የተሳናቸውና የአካል ጉዳተኞች ለማዘጋጀት ከየካ ክፍለ ከተማ ጋር የአርማ ርክክብ አድርጓል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የመደመር መንግስት የወጣቶች የፖናል ውይይት ተካሄደ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በጠቅላይ ሚኒስቴር ዳ/ር አብይ አሕመድ በተፃፈው መደመር መንግስት መፅሐፍ ፅንሰ ሀሳብ ላይ ያተኮረ የወጣቶች የፖናል ውይይት አካሂዷል። በፖናል ውይይቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ አቶ ክብርዓለም ደምሴ የመደመር መንግስት መፃሀፍ በሀገር በቀል እሳቤዎች የተዋቀረ ለሀገራዊ ችግሮች ሀገራዊ መፍትሔዎችን ያመላከተ መፅሐፍ ነው ብለዋል። መደመር፣ የመደመር መንገድ ፣ የመደመር ትውልድና የመደመር መንግስት መፅሀፎች ነገን የሚያሳዩና ብሩህ ተስፋን የሚፈነጥቁ ሀገራዊ ፋይዳቸው የጎሉ መሆናቸውን አቶ ክብረአለም ገልፀዋል። በሌላ በኩል ለፖናል ውይይቱ መነሻ ሐሳብ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ከተማ የብልፅግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ሀላፊ አቶ ዳዊት ምንዳዬ በበኩላቸው የመደመር እሳቤ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እሳቤ መሆኑን ገልፀዋል። የመደመር መንግስት መፅሀፍ ተግባራትን በቅንጅት በማከናወን ለችግሮች ከራስ የመነጨ መፍትሔ በማስቀመጥ ለሀገር ብልፅግና ለመትጋት የሚያነሳሳ መሆኑን አቶ ዳዊት ተናግረዋል። የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በፍቃዱ እንደተናገሩት የመደመር መንግስት መፅሀፍ ነገን የተሻለ ለማድረግ ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣና ለሀገር ብልፅግና እንዲተጋ መንገዶችን ያመላከተ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ አንተነህ አክለውም አቅምን መጠቀም፣ ምዕናብን ከፍ ማድረግ፣ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ያስገኘው ውጤትና የፖለቲካ ባህልን ማሻሻል ይገባል ብለው ወጣቶች በሀገራቸው ሁለንተናዊ ብልፅግና አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸውም ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በመደመር መንግሰት የወጣቶች የፖናል ውይይት በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚካሄድ ይሆናል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ''በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጲያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃልየደም ልገሳ መርሃ-ግብር አካሄደ።

የልደታ ክፍለ ከተማ የወጣቶች ክንፍ የክፍለ ከተማ ወጣቶችን በማስተባበር በሜክሲኮ አደባባይ 150 በላይ ወጣቶች የደም ልገሳ አካሂደዋል ። የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሳሙኤል ዋለልኝ እንደገለፀው የሰው ህይወት ለማዳን የወጣቶች ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዉ የልደታ ብልፅግ ፓርቲ ወጣቶች በክረምት በጎ ፍቃድ መርሀ ግብሩ ከፍተኛ የሆነ ተግባራትን እያከናወኑ ሲሆን የዛሬዉ የደም ልገሳ በሁሉም ወረዳዎች ሲካሄድ የነበረ እና የሚቀጥል ሲሆን ወጣቶች ከደም ልገሳ ከማድረግ ባለፈ የአካባቢያቸውን ሰላም ከማረጋገጥና ስራ ፈጥረው በመስራት እና የስራ ባህልን በማዳበር ሰርቶ መለወጥን ባህሉ ያደረገ ወጣት መፍጠርና በማንኛውም አግባብ ለበጎ ተግባር ፊት የሚቆም ወጣቶች ማፍራት ላይ በርካታ ስራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

image
image
image
image