Welcome to Lideta Subcity Youth and Sport Office!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ህብረተሰብ እና ተወዳዳሪና ውጤታማ የሆነ ስፖርተኛ ተፈጥሮ ለማየት ይተጋል!!
image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ''በጎነት እና አብሮነት ለኢትዮጲያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃልየደም ልገሳ መርሃ-ግብር አካሄደ።

ነሀሴ 11, 2018
የልደታ ክፍለ ከተማ የወጣቶች ክንፍ የክፍለ ከተማ ወጣቶችን በማስተባበር በሜክሲኮ አደባባይ 150 በላይ ወጣቶች የደም ልገሳ አካሂደዋል ። የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሳሙኤል ዋለልኝ እንደገለፀው የሰው ህይወት ለማዳን የወጣቶች ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዉ የልደታ ብልፅግ ፓርቲ ወጣቶች በክረምት በጎ ፍቃድ መርሀ ግብሩ ከፍተኛ የሆነ ተግባራትን እያከናወኑ ሲሆን የዛሬዉ የደም ልገሳ በሁሉም ወረዳዎች ሲካሄድ የነበረ እና የሚቀጥል ሲሆን ወጣቶች ከደም ልገሳ ከማድረግ ባለፈ የአካባቢያቸውን ሰላም ከማረጋገጥና ስራ ፈጥረው በመስራት እና የስራ ባህልን በማዳበር ሰርቶ መለወጥን ባህሉ ያደረገ ወጣት መፍጠርና በማንኛውም አግባብ ለበጎ ተግባር ፊት የሚቆም ወጣቶች ማፍራት ላይ በርካታ ስራዎች እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች