Welcome to Lideta Subcity Youth and Sport Office!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ህብረተሰብ እና ተወዳዳሪና ውጤታማ የሆነ ስፖርተኛ ተፈጥሮ ለማየት ይተጋል!!
image
image
image
image
image

በ15ኛው ከተማ አቀፍ የአካል ጉዳተኞችና መስማት የተሳናቸው ስፖርታዊ ውድድርና ፌስቲቫል ተሳታፊ የነበረው የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች 2ኛ ደረጃ በመያዝ ተሸላሚ ሆነ።

ህዳር 27, 2018
እንኳን ደስ አላቹህ!! 27 ወርቅ፣ 18 ብር እና 12 የነሀስ መዳሊያዎች በመሰብሰብ የልደታ ክ/ከተማ 2ኛ ሆኖ ወድድሩን አጠናቋል። የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በሽብርቅ ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች 1ኛ ሆኖ አጠናቋል። በተገኘው ውጤት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ይህ ውጤት እንዲመጣ ስትሰሩ ለነበራቹህ እና ለክፍለ ከተማው ነዋሪዎች እንኳን ደስ አላቹህ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም "በአዲስ ዕይታ የልደታን ከፍታ ማረጋገጥ" የሚል መርህን ይዘን በሁሉም ዘርፍ ውጤት ለማምጣት እየሰራን ነው ብለዋል። ክ/ከተማው 16ኛውን መስማት የተሳናቸውና የአካል ጉዳተኞች ለማዘጋጀት ከየካ ክፍለ ከተማ ጋር የአርማ ርክክብ አድርጓል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች